የገቢዎች ባለስልጣን ኃላፊ አቶ ያሲን አብዱላህ የመክፈቻ ንግግር አድገዉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ከፍተዋል ። አቶ ያሲን የስልጠና መድረኩን ስከፍቱ በ2018 በጀት ዓመት የተለጠጠ የገቢ ዕቅድ መያዙን ገልፀው ዕቅዱ እንዲሳካ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መስራት አለባቸው በማለት ገልጸዋል ።
የመሬት ይዞታ መረጃና ምዝገባ ኤጀንሲ ሃላፊ አቶ ኢብራሂም አህመድ እንደገለፁት የስልጠናው አስፈላጊነትን በተመለከተ የ2018 ዕቅድ የበለጠ በውጤታማነት ለመፈጸም በሶስቱ (በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ፤ በገቢዎች ባለስልጣን ና ማዘጋጃ ቤት)ተቋማት መካካል በ2017 በጀት አመት የነበረውን ቅንጂታዊ አሰራር ይበልጥ በቴክኒካል ባለሙያዎች ዘንድ በማጎልበት መስራት የሚያስፈልግ መሆኑን በመግለጽ የዛሬው ስልጠና ይህ እንዲዳብር ወሳኝ ነው ብለዋል ። አክለውም የከተማ ቦታ ኪራይና የከተማ ቤት ግብር ገቢ አሰባሰብ ያጋጠማቸው ችግሮችን በመለየት ለቀጣይ የ2018 በጀት አመት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል ።
በመድረኩም የከተማ ቦታ ኪራይና የከተማ ቤት ግብር የ2017 አፈጻጸም በአቶ ሻምበል አስፋው ቀርቧል ። በቀረበው ሰነድ ዙሪያም በመድረኩ የተገኙ ባለሞያዎች አስተያየት እና ጥያቄዎች በማንሳት ተወያይተው በመጨረሻም የስራ አቅጣጫ አስቀምጧል ።
ሐምሌ 25/2017 ዓ.ም







