Thursday, April 30, 2026
HomeNews & EventDevelopmentየሐረር ከተማ ዲጂታል አድራሻ ስርአት ትግበራ በከተማችን ዋና ዋና መንገዶች ላይ አቅጣጫ...

የሐረር ከተማ ዲጂታል አድራሻ ስርአት ትግበራ በከተማችን ዋና ዋና መንገዶች ላይ አቅጣጫ ጠቋሚ (ታፔላ) የመትከልና የሰፈር እና የመንገድ ቁጥር የይዙ ፕለቶችን የመለጠፍ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

የመሬት ይዞታ መረጃና ምዝገባ ኤጀንሲ በመንገድ ዳር ለሚተከሉ የሰፈር እና የመንገድ ላይ ቁጥር መለጠፊያ ምሶሶዎችን በከተማችን ዋና ዋና መንገዶች ላይ የመትከል ስራ እየተሰራ ይገኛል ።

በተተከሉት ፖሎች ላይ የሰፈሮቹ ዲጂታል አድራሻ ቁጥር በቀላሉ ከሩቅም ከቅርብም በሚታይ መልኩ በሰማያዊ እና በአረንጓዴ ቀለም ታፔላ የታሰረ ሲሆን ሰማያዊው ታፔላ የሰፈር /Neighborhood / ቁጥሮችን የሚያሳይ ሲሆን በተጨማሪም በየሰፈሩ ውስጥ የሚገኙትን የቤት ቁጥር Range ከስንት እስከ ስንት እንደሚገኝ ይጠቁማል። አረንጓዴው ታፔላ በተመሳሳይ መንገዶችን አድራሻ የሚጠቁም ሆኖ ከ Principal Arterial ዋናው ከአዲስ አበባ ወደ ጂግጂጋ የሚሄደው የፌደራል መንገድ አንስቶ በከተማው ውስጥ የሚገኙትን ሁሉንም የመንገድ አይነቶች የሚያመላክት ይሆናል ። በመሆኑም ጎዳና/Avenue /፥ መንገድ /Street/፥ ንኡስ መንገድ /Sub Street/፥ የግል መንገድ/Private Road/፥ እንዲሁም የዘላቂ ያልሆኑ/Cul da sacs/ መንገዶችን የሚያመላክት ይሆናል።

በከተማችን እየተተገበረ የሚገኘው የዲጂታል አድራሻ ስርአት ትግበራ እንደሚታወቀው በተመረጡ ሰፈሮች ውስጥ የቤት ቁጥር የመለጠፍ ስራ የተከናወነ ሲሆን ፤ ባለይዞታዎች እንዲሁም እንግዶች እነዚህን አድራሻዎች በመጠቀም በቀላሉ የተለያዩ አገልግሎቶችን የቱሪስት መዳረሻዎችን ፣ የግብይት ፣ የናቪጌሽን፣ የመንገድና አቅጣጫን የመለየት፣ የባንክ አገልግልት ፣ የፍሳሽ አገልግልት፣ የመብራት፣ የውሃ አቅርቦት አገልግልት፣ የሆስፒታል፣ የፖሊስ፣ የእሳት አደጋ መከላከል ፣ የአምቡሊንስ፣ እና ሌሎች በርካታ አገልግሎቶች ተደራሽ እንዲሆን ያደርጋል ።

RELATED ARTICLES

Most Popular

Recent Comments