በዛሬው እለት በክልላችን በመንግስት እና በግል ዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጐብኝተናል።
በአብዛኛው ፕሮጀክቶች አፈፃፀም መሻሻል የታየባቸው ቢሆኑም አንዳንድ የመንግስት እና የግል ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች አዝጋሚ እንደሆኑ ተመልክተናል።
ስለሆነም በቀጣይ ጊዜያት በመንግስት ፕሮጀክቶች ማነቆ የሆኑ ችግሮችን በመቅረፍ ርብርብ የምናደርግ ሲሆን በግል ኢንቨስትመንቱ ዘርፍ የመንግስትና የህዝብ ሀብት የሆነውን መሬት በምደባ ወስደው ለአመታት ሳያለሙ በቆዩ አካላት ላይ አስተማሪ እርምጃ የሚወሰድ ይሆናል።






