የከተማ ልማትና ኮንስተራክሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙኽታር ሳሊህ የተቋሙ የ2017 የ9 ወር እቅድ አፈጻጸም ከማኔጅመንት አባላት ጋር ላለፉት ሁለት ቀናት በክልሉ አስፈፃሚ ተቋማት፤የክልሉ ሴክተር መ/ቤቶች እና ወረዳዎች ባደረጉት የግምገማ መድረክ የተነሱ ሀሳቦች እና በክቡር ፕሬዝዳንት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አካሂደዋል ።በውይይቱ በዋናነት የአገልግሎት አሰጣጥና መልካም አስተዳደር ተግባራት በማዘመንና በማሳለጥ የተሻለ አፈጻጸም እንዲኖር ፤ ገቢን ከማሳደግ አንፃር በትኩረትና በትጋት እንዲሰራ እንዲሁም በዚህ 9 ወር ሳይሰሩ የቆዩ እና የተንጠባጠቡ ስራዎችን ለይቶ በቀሪ ግዜ ውስጥ እቅድ ሪቫይዝ በማረግ መፈጸም እንደሚገባ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን ከወዲሁ የ 2017 ማጠቃለያ እና የ2018 በጀት አመት የዝግጅት ምዕራፍ ዝግጅት እንዲደረግ በማለት የከተማ ልማትና ኮንስተራክሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙኽታር ሳሊህ አሳስበዋል ።በመጨረሻም ስራዎች በቀጣይ በቀሪ 3 ወራት በርብርብ በጥራትና በፍጥነት እንዲሰሩ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል ፡፡










